መጽሐፈ ዕዝራ።

1 2 3 4 5 6 7 8 9 10


ምዕራፍ 2

የባቢሎንም ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው የተመለሱት የአገር ልጆች እነዚህ ናቸው።
2 ፤ ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከሠራያ፥ ከረዕላያ፥ ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥ ከመሴፋር፥ ከበጉዋይ፥ ከሬሁም፥ ከበዓና ጋር መጡ።
3 ፤ የእስራኤልም ሕዝብ ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤ የፋሮስ ልጆች፥ ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት።
4 ፤ የሰፋጥያስ ልጆች፥ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት።
5 ፤ የኤራ ልጆች፥ ሰባት መቶ ሰባ አምስት።
6 ፤ ከኢያሱና ከኢዮአብ ልጆች የሆኑ የፈሐት ሞዓብ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ አሥራ ሁለት።
7 ፤ የኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት።
8 ፤ የዛቱዕ ልጆች፥ ዘጠኝ መቶ አርባ አምስት።
9 ፤ የዘካይ ልጆች ሰባት መቶ ስድሳ።
10 ፤ የባኒ ልጆች፥ ስድስት መቶ አርባ ሁለት።
11 ፤ የቤባይ ልጆች፥ ስድስት መቶ ሀያ ሦስት።
12 ፤ የዓዝጋድ ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ ሀያ ሁለት።
13 ፤ የአዶኒቃም ልጆች፥ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት።
14 ፤ የበጉዋይ ልጆች፥ ሁለት ሺህ አምሳ ስድስት።
15 ፤ የዓዲን ልጆች፥ አራት መቶ አምሳ አራት።
16 ፤ ከሕዝቅያስ ወገን የአጤር ልጆች፥ ዘጠና ስምንት።
17 ፤ የቤሳይ ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ ሦስት።
18 ፤ የዮራ ልጆች፥ መቶ አሥራ ሁለት።
19 ፤ የሐሱም ልጆች፥ ሁለት መቶ ሀያ ሦስት።
20
21 ፤ የጋቤር ልጆች፥ ዘጠና አምስት። የቤተ ልሔም ልጆች፥ መቶ ሀያ ሦስት።
22 ፤ የነጦፋ ሰዎች፥ አምሳ ስድስት።
23 ፤ የዓናቶት ሰዎች፥ መቶ ሀያ ስምንት።
24 ፤ የዓዝሞት ልጆች፥ አርባ ሁለት።
25 ፤ የቂርያትይዓሪምና የከፊራ የብኤሮትም ልጆች፥ ሰባት መቶ አርባ ሦስት።
26 ፤ የራማና የጌባ ልጆች፥ ስድስት መቶ ሀያ አንድ።
27 ፤ የማክማስ ሰዎች፥ መቶ ሀያ ሁለት።
28 ፤ የቤቴልና የጋይ ሰዎች፥ ሁለት መቶ ሀያ ሦስት።
29 ፤ የናባው ልጆች፥ አምሳ ሁለት።
30 ፤ የመጌብስ ልጆች፥ መቶ አምሳ ስድስት።
31 ፤ የሁለተኛውም ኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት።
32 ፤ የካሪም ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ።
33 ፤ የሎድና የሐዲድ የኦኖም ልጆች፥ ሰባት መቶ ሀያ አምስት።
34 ፤ የኢያሪኮ ልጆች፥ ሦስት መቶ አርባ አምስት።
35 ፤ የሴናዓ ልጆች፥ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ሠላሳ።
36 ፤ ካህናቱ፤ ከኢያሱ ወገን የዮዳኤ ልጆች፥ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት።
37 ፤ የኢሜር ልጆች፥ ሺህ አምሳ ሁለት።
38 ፤ የፋስኮር ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት።
39 ፤ የካሪም ልጆች፥ ሺህ አሥራ ሰባት።
40 ፤ ሌዋውያኑ፤ ከሆዳይዋ ወገን የኢያሱና የቀድምኤል ልጆች፥ ሰባ አራት።
41 ፤ መዘምራኑ፤ የአሳፍ ልጆች፥ መቶ ሀያ ስምንት።
42 ፤ የበረኞች ልጆች፤ የሰሎም ልጆች፥ የአጤር ልጆች፥ የጤልሞን ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የሐጢጣ ልጆች፥ የሶባይ ልጆች፥ ሁሉ መቶ ሠላሳ ዘጠኝ።
43 ፤ ናታኒም፤ የሲሐ ልጆች፥ የሐሡፋ ልጆች፥
44 ፤ የጠብዖት ልጆች፥ የኬራስ ልጆች፥ የሲዓ ልጆች፤
45 ፤ የፋዶን ልጆች፥ የልባና ልጆች፥
46 ፤ የአጋባ ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የአጋብ ልጆች፥ የሰምላይ ልጆች፥ የሐናን ልጆች፥
47 ፤ የጌዴል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥ የራያ ልጆች፥
48 ፤ የረአሶን ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥
49 ፤ የጋሴም ልጆች፥ የዖዛ ልጆች፥ የፋሴሐ ልጆች፥
50 ፤ የቤሳይ ልጆች፥ የአስና ልጆች፥ የምዑናውያን ልጆች፥ የንፉሰሲም ልጆች፥
51 ፤ የበቅቡቅ ልጆች፥ የሐቁፋ ልጆች፥ የሐርሑር ልጆች፥
52 ፤ የበስሎት ልጆች፥ የምሒዳ ልጆች፥
53 ፤ የሐርሳ ልጆች፥ የበርቆስ ልጆች፥
54 ፤ የሲሣራ ልጆች፥ የቴማ ልጆች፥ የንስያ ልጆች፥ የሐጢፋ ልጆች።
55 ፤ የሰሎሞንም ባሪያዎች ልጆች፤ የሶጣይ ልጆች፥ የሶፌሬት ልጆች፥ የፍሩዳ ልጆች፥
56 ፤ የየዕላ ልጆች፥ የደርቆን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥
57 ፤ የሰፋጥያስ ልጆች፥ የሐጢል ልጆች፥ የፈክራት ልጆች፥ የሐፂቦይም ልጆች፥ የአሚ ልጆች።
58 ፤ እነዚህ ናታኒም ሁሉና የሰሎሞን ባሪያዎች ልጆች ሦስት መቶ ዘጠና ሁለት ነበሩ።
59 ፤ ከቴልሜላ፥ ከቴላሬሳ፥ ከክሩብ፥ ከአዳን፥ ከኢሜር የወጡ እነዚህ ነበሩ፤ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም፤
60 ፤ የዳላያ ልጆች፥ የጦብያ ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ ሁለት ነበሩ።
61 ፤ ከካህናቱም ልጆች፤ የኤብያ ልጆች፥ የአቆስ ልጆች፥ ከገለዓዳዊው ከቤርዜሊ ልጆች ሚስት ያገባ፥ በስሙም የተጠራ የቤርዜሊ ልጆች።
62 ፤ እነዚህ በትውልድ መጽሐፍ ትውልዳቸውን ፈለጉ፤ ነገር ግን አልተገኘም፥ ከክህነትም ተከለከሉ።
63 ፤ ሐቴርሰታም። በኡሪምና በቱሚም የሚፈርድ ካህን እስኪነሣ ድረስ ከቅዱሰ ቅዱሳን አትበሉም አላቸው።
64
65 ፤ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ከነበሩ ከሎሌዎቻቸውና ከገረዶቻቸው ሌላ ጉባኤው ሁሉ አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ። ሁለት መቶም ወንዶችና ሴቶች መዘምራን ነበሩአቸው።
66 ፤ ፈረሶቻቸውም ሰባት መቶ ሠላሳ ስድስት በቅሎቻቸውም ሁለት መቶ አርባ አምስት፥
67 ፤ ግመሎቻቸውም አራት መቶ ሠላሳ አምስት፥ አህዮቻቸውም ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሀያ ነበሩ።
68 ፤ በኢየሩሳሌምም ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤት በመጡ ጊዜ ከአባቶች ቤቶች አለቆች አያሌዎች ለእግዚአብሔር ቤት በስፍራው ይሠራ ዘንድ በፈቃዳቸው ሰጡ።
69 ፤ ስድሳ አንድ ሺህም የወርቅ ዳሪክ፥ አምስት ሺህም ምናን ብር፥ አንድ መቶም የካህናት ልብስ እንደ ችሎታቸው ወደ ሥራው ቤተ መዛግብት አቀረቡ።
70 ፤ ካህናቱና ሌዋውያኑም፥ ከሕዝቡም አያሌዎች፥ መዘምራኑና በረኞቹም፥ ናታኒምም በከተሞቻቸው፥ እስራኤልም ሁሉ በከተሞቻቸው ተቀመጡ።